ሰባት የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በደቡብ አፍሪካ ጠፉ

Date:

የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን ለ2019 (እ.ኤ.አ 2027) የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ታሪካዊ በሆነ ሁኔታ ለምድብ ድልድል ካለፈ በኋላ፣ ሰባት ተጫዋቾች ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆኑ በደቡብ አፍሪካ መቅረታቸውን ቢኤስኤን ስፖርትስ ዘግቧል።

​ይህ ክስተት የተሰማው ኤርትራ በድምር ውጤት ኤስዋቲኒን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ፣ ከ19 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል መሸጋገሯን ካረጋገጠች ጥቂት ቆይታ በኋላ ነው።

​እንደ ዘገባው ከሆነ ለጨዋታው ወደ ደቡብ አፍሪካ ከተጓዙት አሥር በአገር ውስጥ የሚጫወቱ ተጫዋቾች መካከል ወደ ኤርትራ የተመለሱት ሦስቱ ብቻ ናቸው። ወደ ሀገራቸው የተመለሱት ተጫዋቾች አብሌሎም ተክለዝጊ፣ ናሆም ታደሰ እና ሮሜል አብዱ ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ ሰባት ተጫዋቾች በደቡብ አፍሪካ መቅረታቸው ተነግሯል።

​ይህ ድርጊት የኤርትራ ስፖርተኞች ለዓለም አቀፍ ውድድሮች ወደ ውጭ ሀገራት በሚጓዙበት ወቅት የግል እና ፖለቲካዊ ምክንያቶችን በመጥቀስ በዚያው የመቅረት (ጥገኝነት የመጠየቅ) ልማዳቸው ላይ አዲስ ስጋትን ፈጥሯል።

​ኤርትራ ወደ ምድብ ድልድሉ ማለፏ ለሀገሪቱ የእግር ኳስ እድገት ትልቅ ስኬት ተደርጎ ሲወደስ የቆየ ቢሆንም፣ የተጫዋቾቹ ድንገተኛ መሰወር ለቡድኑ ከፍተኛ እንቅፋት እንደሚሆን ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በመንገድ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ

አደጋው የደረሰው ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ...

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...