የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም በነበሩት ሶስት ወራት ውስጥ በኢትዮጵያ ለሚገኘው የቴሌኮም ድርጅቱ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን የኬንያ ሺሊንግ በካፒታል መልክ ማፍሰሱን ገለጸ።
ድርጅቱ ባወጣው አዲስ ይፋዊ መግለጫ መሠረት፣ በኢትዮጵያ ለሚንቀሳቀሰው ቅርንጫፉ ያደረገው ጠቅላላ የፋይናንስ አስተዋፅኦ ባለፈው መጋቢት ወር ከነበረበት 158.2 ቢሊዮን ሺሊንግ (1.223 ቢሊዮን ዶላር)፣ በሰኔ ወር መጨረሻ ወደ 159.6 ቢሊዮን ሺሊንግ (1.234 ቢሊዮን ዶላር) አድጓል።
ይህ የካፒታል ጭማሪ ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ባለው የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ያለውን ከፍተኛ ትኩረትና ቁርጠኝነት ያሳያል ተብሏል።
ኩባንያው ይህንን ስራ የሚከውነው ከዋናው ባለድርሻ ቮዳኮም፣ ከሱሚቶሞ ኮርፖሬሽን፣ ከብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት እና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ በመሆን ነው።
ይህ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ድርጅቱ በአገሪቱ የሚያደርገውን የኔትወርክ ማስፋፊያ፣ የአገልግሎት ጥራት ማሻሻል እና የደንበኞችን ቁጥር የማሳደግ ስራ በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል የሚረዳው መሆኑ ተመልክቷል።
