የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯን ፍፁም አሰፋን (ዶ/ር)፣ የፍትህ ሚኒስትሯን ወ/ሮ ሃና አርአያሰላሴን እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑትን ዘለቀ ተመስገንን (ዶ/ር) የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል አድርጎ መሾሙን ዛሬ አስታውቋል።
ተቋሙ በሰጠው መግለጫ እነዚህ ሶስት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በመንግስት፣ በልማት እና በኢንቨስትመንት ዘርፎች ያካበቱት ሰፊ ልምድና አመራር፣ ኢትዮጵያ በስትራቴጂካዊ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢንቨስትመንቶች እንዲሁም በፖርትፎሊዮ አስተዳደር የኢኮኖሚ ለውጥን በማፋጠን ረገድ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ገልጿል።
CapitalNews
