መንግስት በነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ ላይ በሌትር እስከ ስምንት ብር የሚደርስ ጭማሪ ማድረጉ ተገለጸ፡፡ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደረገ፡፡ በዓለም ገበያ የታየውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መነሻ በማድረግ ከመስከረም 28/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በሥራ ላይ የሚቆይ የሁሉም የነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደርጓል ሲል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። በዚህ መሰረት፦ ቤንዚን – ብር 91.14 በሊትር፣ ነጭ ናፍጣ – ብር 90.28 በሊትር፣ ኬሮሲን – ብር 90.28 በሊትር፣ ቀላል ጥቁር ናፍጣ – ብር 100.20 በሊትር፣ ከባድ ጥቁር ናፍጣ – ብር 97.67 በሊትር የኾነ ሲኾን የአውሮፕላን ነዳጅ ደግሞ በሊትር 77.76 ብር መኾኑ ተገልጽል።
