በሊትር እስከ 8ብር የሚደርስ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ተደረገ

Date:

መንግስት በነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ ላይ በሌትር እስከ ስምንት ብር የሚደርስ ጭማሪ ማድረጉ ተገለጸ፡፡ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደረገ፡፡ በዓለም ገበያ የታየውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መነሻ በማድረግ ከመስከረም 28/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በሥራ ላይ የሚቆይ የሁሉም የነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደርጓል ሲል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። በዚህ መሰረት፦ ቤንዚን – ብር 91.14 በሊትር፣ ነጭ ናፍጣ – ብር 90.28 በሊትር፣ ኬሮሲን – ብር 90.28 በሊትር፣ ቀላል ጥቁር ናፍጣ – ብር 100.20 በሊትር፣ ከባድ ጥቁር ናፍጣ – ብር 97.67 በሊትር  የኾነ ሲኾን የአውሮፕላን ነዳጅ ደግሞ በሊትር 77.76 ብር መኾኑ ተገልጽል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...