በሳውዲ ከ1900 በላይ ኢትዮጵያዊ እስረኞች በምህረት ተለቀቁ

Date:

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በ በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ጉዳይ በተመለከተ 1971 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን የሳዑዲ ባለሥልጣናት ካደረጉት የንጉሣዊ ምሕረት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግሥትም እነዚህን ዜጎች ወደ አገራቸው በተከታታይ በረራዎች እየመለሰ የሚገኝ ሲሆን ሚኒስቴሩ ይህንን ሒደት በቆንስላና በሰብዓዊ ጉዳዮች ላይ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ትብብርና የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚያንጸባርቅ መሆኑንም አመልክቷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በውጭ አገር የሚኖሩ የኢትዮጵያውያንን ጥቅሞች፣ መብቶችና ደኅንነት ለመጠበቅ ያሉትን የዲፕሎማሲና የቆንስላ አማራጮች ሁሉ መጠቀሙን እደሚቀጥልም አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...