በሳውዲ ከ1900 በላይ ኢትዮጵያዊ እስረኞች በምህረት ተለቀቁ

Date:

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በ በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ጉዳይ በተመለከተ 1971 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን የሳዑዲ ባለሥልጣናት ካደረጉት የንጉሣዊ ምሕረት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግሥትም እነዚህን ዜጎች ወደ አገራቸው በተከታታይ በረራዎች እየመለሰ የሚገኝ ሲሆን ሚኒስቴሩ ይህንን ሒደት በቆንስላና በሰብዓዊ ጉዳዮች ላይ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ትብብርና የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚያንጸባርቅ መሆኑንም አመልክቷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በውጭ አገር የሚኖሩ የኢትዮጵያውያንን ጥቅሞች፣ መብቶችና ደኅንነት ለመጠበቅ ያሉትን የዲፕሎማሲና የቆንስላ አማራጮች ሁሉ መጠቀሙን እደሚቀጥልም አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...