በኢትዮጲያ የሚገኙ የደም ባንኮች ቁጥር 59 ደረሰ

Date:

በተለያዩ ክልሎች ሙሉ አቅም አዳዲስ የደም ባንኮች  እየተገነቡ መሆኑን እና ይህም የበጎ ፍቃድ ደም ለጋሾችን ቁጥር በማሳደግ በደም እጥረት ጉዳት እንዳይደርስ ከማድረጉም ባሻገር  የደም ባንክን ተደራሽነት ይጨምራል ሲሉ የኢትዮጲያ ደም እና ህብረህዋስ ባንክ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ታረቀኝ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

በኢትዮጲያ ተጨባጭ ሁኔታ በደም ባንክ ተደራሽነት ላይ ወደ ፊት በጥናት እየታየ መሰራት አለበት ያሉት አቶ አለማየሁ በዘንድሮ በጀት አመት በ3 ክልሎች ብቻ በራስ አቅም 10 የደም ባንኮችን ለመገንባት ታቅዶ 6 ያህሉን አጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ተሰርገዋል።

የአሮሚያ ክልል በዘንድሮው የበጀት አመት አራት የደም ባንኮችን ለመገንባት አቅዶ የደምቢ ዶሎና  የሻምቡ የደም ባንኮችን አስመርቆ ለአገልግሎት ማብቃቱን ገልፀው፤በተመሣሣይ የሱማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት  በክልሉ የሚገኙትን የደም ባንኮች ቁጥር ከ7 ወደ 12 ለማድረስ አቅዶ ፊልቱ፣ ቀብሪደሃርና  ገርቦ የደም ባንኮችን የገነባ ሲሆን የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትም የአብአላ ደም ባንክን በመገንባት በክልሉ የሚገኙ የደም ባንኮች ቁጥር 3 ማድረስ ተችሏል።

በአጠቃላይ የደም ባንኮች ግንባታ በሀገሪቱ የሚገኙ የደም ባንኮችን ቁጥር ወደ 59 ማድረሱን የጠቆሙ ሲሆን ይህም በጎ ፍቃድ ደም ለጋሾች በአቅራቢያቸው በመሄድ ደም በመለገስ በደም እጦት ምክንያት ሊጠፉ የሚችሉ ህይወቶችን ለመታደግ አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥርላቸው እና የሀገሪቱ የጤና ሥርዓት መሻሻል አዎንታዊ ሚና እንዳለዉ ተመላክቷል፡፡

#BisratRadio

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...