በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ዳግም ጦርነትእንዳይቀሰቀስ ዲፕሎማቶች አሳሰቡ

Date:

በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከወዲሁ መግታት እንደሚገባ የአሜሪካና አውሮፓ ዲፕሎማቶች አሳሰቡ፡፡

የአፍሪካ ቀንድ ምክትል ልዩ መልዕክተኛ የነበሩት ፓይተን ኖፍ እና የቀይ ባህር የጥናት ማዕከል ሊቀመንበር አሌክሳንደር ሮንዶስ፣ በሁለቱ ጎረቤት ሀገራት መካከል የሚስተዋለውን ውጥረት አስመልክተው፣ ፎሬይን ፖሊሲ መጽሔት ላይ ሀሳባቸውን አጋርተዋል፡፡

በሁለቱም በኩል የሚስተዋሉ የቃላት ልውውጦችና የጦርነት ዝግጅቶች በሀገራቱ መካከል ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል አመላካች እንደሆኑ ዲፕሎማቶቹ ጠቁመዋል፡፡

በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ያለው ፍጥጫ ወደ ጦርነት የሚያድግ ከሆነ ሰሜን ምስራቅ አፍሪካንና በጂኦፖለቲካዊ ጠቀሜታው ወሳኝ የሆነው ቀይ ባህር ላይም ችግር ሊጋርጥ እንደሚችል አመልክተዋል፡፡

አለም በሰፊ አህጉራዊና አለምአቀፋዊ ስርዓት አልበኝነት እየተናጠች በምትገኝበት በዚህ ወቅት፣ በትግራይ ያለው የፖለቲካና የጸጥታ ሁኔታ መበላሸት በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ጦርነትን ሊያስከትል እንደሚችልም አሳስበዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...