በኢትዮጵያ የመጀመሪያው LEGO መደብር ተከፈተ

Date:

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው LEGO የሕጻናት መጫወቻ ዕቃዎች መሸጫ መደብር ተከፍቷል። በመደብሩ ለሽያጭ የቀረቡ የመጫወቻ ዕቃዎች የሕጻናትን የፈጠራ አቅም የሚያሳድጉ ናቸው ተብሏል።

ዛሬ አራት ኪሎ በሚገኘው አምባሳደር ሞል፣ ሶስተኛ ፎቅ ላይ ተመርቆ ስራውን የጀመረው የተለያዩ የLEGO ምርት የሆኑ የሕጻናት መጫወቻ ዕቃዎችን የያዘው መደብሩ፣ ከዕቃዎች ሽያጭ ባሻገር ሕጻናት የቡድን ስራ እና ጥበባዊ አገላለጾችን በጨዋታ ማሰስ የሚችሉበት የመማሪያ ማዕከል ስለመሆኑ ተነግሯል።

በምረቃ መረሐ ግብሩ ላይ ጨዋታ ዓለምአቀፋዊ ቋንቋ ስለመሆኑ ሲነገር፣ ይህ የLEGO መደብር ዓለምአቀፋዊውን ቋንቋ ለየት ባሉ አማራጮች ለኢትዮጵያ ሕጻናት ለማስተዋወቅ ጥረት እንደሚደረግ ለማወቅ ተችሏል።

የሴቶች እና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ሱኔ ክሮግስትራፕ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ዕንግዶች በምረቃ መረሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ነበር።

LEGO ተቀማጭነቱን በዴንማርክ ያደረገ የሕጻናት መጫወቻ ማምረቻ ድርጅት ሲሆን፣ በዓለምአቀፍ ደረጃ በተለያዩ አገራት የሕጻናት የመዝናኛ መንደሮችን ገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት በማድረግ የሚታወቅ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...