በጎርጎሮሳውያኑ 2024 በኢትዮጵያ 43 ጋዜጠኞች ለእገታ እና እስር መዳረጋቸውን ሪፖርት አመለከተ

Date:

የጋዜጠኞች ደህንነት ግምገማ በማካሄድ የሚታወቀው አለም አቀፉ የሚዲያ ድጋፍ ተቋም ባወጣው ሪፖርት በኢትዮጵያ በጎርጎሮሳውያኑ 2024 ብቻ 43 ጋዜጠኞች ለእገታ እና እስር መዳረጋቸውን አስታወቀ። ሪፖርቱ ጋዜጠኞች ከመንግስት እና መንግስትዊ ካልሆኑ አካላት ማስፈራሪያ፣ እስር እና እንግልትን ጨምሮ ለበርካታ ጫናዎች ተጋላጭ መሆናቸውን አመላክቷል።

ከ60 ጋዜጠኞች ጋር በተደረገ ቃለ መጠይቅ እና በሰነድ በተመዘገቡ ጉዳዮች ላይ የተመሠረተው ሪፖርቱ፣ በግጭት በተጎዱ አካባቢዎች ያሉ ጋዜጠኞች በተለይም በ አማራ፣ ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ከፍተኛ አደጋ እንደሚገጥሟቸው አረጋግጧል።

በሪፖርቱ መሠረትም “የታጠቁ ቡድኖች ጋዜጠኞችን የቤዛ ክፍያ ለመቀበል ወይም ስለግጭቶች የሚወጡትን የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎችን ለመቆጣጠር እንዲሁም ቁሳቁሶቻቸውን ለመወሰድ በማሰብ በዘፈቀደ አስረዋል።  በሌላ በኩል የመንግስት ባለሥልጣናት ደግሞ “ብሔራዊ ደህንነት እና ብሔራዊ ጥቅም” በሚል ሰበስ ጋዜጠኞች እንዲታሰሩ ማድረጋቸውን ሪፖርቱ አመላክቷል።

@ አዲስ ስታንዳርድ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...

በኢትዮጵያ በካንሰር ከሚያዙ ሕፃናት መካከል 75 በመቶ የሚሆኑት ህክምና አያገኙም

በኢትዮጵያ በየዓመቱ በካንሰር ከሚጠቁ ከ6 ሺህ እስከ 8 ሺህ...