ታሜሶል ኮሚኒኬሽን ያዘጋጀው የፋሲካ-ኤክስፖ  ተከፈተ

Date:



የመክፈቻ ስነ ስርዓቱ የፊታችን ማክሰኞ እንደሚከናወን ተነግሯል።

ኤክስፖው “ቴሌ ብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ 2017 ኤክስፖ” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል አስከ ሚያዚያ 11/2017 የሚካሄደው ኤክስፖው ታሜሶል ኮሚኒኬሽን፣ ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን እና ከሊያን ቢዝነስ ግሩኘ ጋር በመሆን አዘጋጅተውታል።

ኤክስፖው ከዚህ ቀደም ከተደረጉ የንግድ ትርኢቶች የተለየ እና ልዩ የሚያደርጉት በርካታ ዝግጅቶች ማቀዱን ተነግሯል።

በቴሌ ብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ ላይ ከ300 በላይ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ንግድ ተቋማት ምርት እና አገልግሎቶቻቸውን  ያቀርባሉ ተብሏል።

ከንግድ ተቋማት በተጨማሪ ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና በልዩ ትኩረት ለአካል ጉዳተኞች እድል፣ በአካል ጉዳተኞች የተመረቱ ምርቶች ለሽያጭ ይቀርባሉ ተብሏል።

በግብይት ወቅት በቴሌብር ለሚከፍሉ 10 በመቶ ተመላሽ እንደሚያገኙም ዛሬ በተሰጠው መግለጫ ላይ ተነግሯል።

ወደ ኤክስፖ ለሚመጡ ጎብኚዎች የተለያዩ የፆም ምግቦች(በብፌ መልክ) በአንድ ቦታ ተዘጋጅቷል ተብሏል።

በኤክስፖው ላይ አንድ የቤት መኪና፣ የሞባይል ቀፎ፣ ሞተር ሳይክል በሽልማት መልክ እንደሚወጡ ተነግሯል።

ታሜሶል ኮሚኒኬሽን የፋሲካ በዓል ዋዜማ ኤክስፖ ጨረታ ያሸነፈው በ60 ሚሊየን ብር  ነው መባሉ ይታወሳል።

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...