የሀገሪቱን የገቢ ንግድ ለማሳለጥ ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሪ ለደንበኞቹ እያቀረበ መሆኑን የገለጸው ንግድ ባንክ፤ በዛሬው ዕለት የደንበቹን የውጪ ምንዛሪ ጥያቄ ለመመለስ 711 ደንበኞቹ ያቀረቡትን ጥያቄዎች በሙሉ በመገምገም ከቀረቡት ጥያቄዎች ውስጥ ለ698 (98%) ያህል ደንበኞቹ በድምሩ የ122.5 ሚሊዮን ዶላር ድልድል የተደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡
የቀሩት ጥቂት ደንበኞችም ጥያቄ ተጨማሪ የመረጃ ማጥራት ሥራ ተሠርቶ በቅርቡ የሚታይላቸው መሆኑን የጠቀመው ባንኩ፤ በቀጣይም ለደንበኞቹ የውጪ ምንዛሪ ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
