የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

Date:

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ፣ የአውሮፓ ህብረት ከአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ሴክሬታሪያት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ሰኞ ዕለት እንደሚፈራረም ታውቋል።

ሚያዚያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚደረገዉ ይህ ስምምነት የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን እና ስምንት አባል ሀገራት በጋራ የሚያከናውኑት የ“ቲም ዩሮፕ ኢንሼቲቭ” አካል ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1.2 ቢሊዮን ዩሮ የሚገመት በጀት ተመድቦለታል።

ጥምረቱ እነዚህ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራትን ማለትም (ዴንማርክ፣ ጀርመን፣ አየርላንድ፣ ፈረንሳይ፣ ኔዘርላንድስ፣ ፊንላንድ፣ ፖርቹጋል እና ስዊድን) በአንድ ላይ ያሰባሰበ ነው።

በአሁኑ ወቅት ከ80 በላይ ንቁ ፕሮጀክቶችን በአባልነቱ የያዘው ይህ ኢኒሼቲቭ፣ የአውሮፓ ህብረት ለአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ውህደት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል።

የስምምነቱ ዋነኛ ዓላማ የአፍሪካን ኢኮኖሚያዊ ውህደት መደገፍ እና የአህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነትን ወደ ተግባር ለማሸጋገር የሚደረገውን ጥረት በገንዘብና በቴክኒክ ማገዝ መሆኑ ተጠቁሟል።

capital news

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...