” አራት ሰው አንድ ቦታ ቀብረናል፤ ከተገደሉት ውስጥ አባትና ልጅ ይገኙበታል ! “

Date:



‎በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ በምስራቅ ጉራጌ ዞን፣ ምስራቅ መስቃን ወረዳ ኢንሰኖ ነዋሪዎች  እንደተናገሩት፣ በኢንሰኖ ዎቻ ገነነ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ሰኔ 25 ሌሊት የታጠቁ ሃይሎች በድጋሚ በፈፀሙት ድንገተኛ ጥቃት 4 ሰዎች ሲሞቱ 7 ሰዎች መቁሰላቸውን ገልፀዋል።

‎ቃላቸውን የሰጡ ሁለት የኢንሰኖ ወረዳ ነዋሪዎች ” ጥቃቱ በቤተሰብ ፕሮግራም ላይ በተሰባሰቡ የቤተሰብ አባላትና ጎረቤታሞች ላይ ነው የደረሰው ” ብለው  ” ከተገደሉት ውስጥ ሁለቱ አባትና ልጅ ናቸው ” ሲሉ አስረድተዋል።

‎ሌላ የአከባቢው ነዋሪም ” ዛሬ አራት ሰው አንድ ቦታ ቀብረናል፣ ባልና ልጇን አንድ ላይ ያጣች እናት እራሷን ስታ ሆስፒታል ገብታለች ” ሲሉ ስለ ጥቃቱ አሰቃቂነት ተናግረዋል።

‎ስለ ቆሰሉ ሰዎች ብዛት ነዋሪዎቹ ሁለት አይነት ቁጥር ያነሱ ሲሆን ከፊሉ 5 ከፊሉ ደግሞ 7 ናቸው ሲሉ ነው አስረድተዋል።

‎ ከምስራቅ ጉራጌ ዞን እና ከምስራቅ ማስቃን ወረዳ ፖሊስ በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነዉ ጥረት ስልክ ባለመስራቱ እና  ባለመነሳቱ ምላሻቸው በዚህ ዘገባ አልተካተተም።

@tikvahethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሁቲዎች በሳዑዲ አውሮፕላን ማረፊያዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

የየመን ሁቲ አማጺያን የሳዑዲ አረቢያን አውሮፕላን ማረፊያዎች እና ሌሎችም...

“የድንቁርና” እና “የታሪክ ፍልሠትን” የሚያስከትል ድርጊት ነው

የቅዱስ ላሊበላ ገዳም ዓለማቀፍ ቅርስ አሥተዳደር ጽሕፈት ቤት፣...

በመቐለ ከተማ በወጣቶች ላይ “የግዳጅ አፈሳ” ተጀምሯል

በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቐለ የጸጥታ ኃይሎች በወጣቶች ላይ...

በትምህርት ቤቶች ዙሪያ የትንባሆ መሸጫ ክልከላ ርቀት ወደ 500 ሜትር ከፍ ተደረገ

የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን በትምህርት ቤቶች ዙሪያ የትንባሆ...