አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

Date:



አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው 50 ሚሊየን ብር ስጦታ ተጨማሪ የሚሆን  ክለባችን ያለበትን የውጪ ተጨዋቾች ደመወዝ ክፍያ፣ወለድ እና ቅጣት መክፈያ የሚሆን ተጨማሪ  26 ሚሊየን ብር  ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓም ገቢ አድርገዋል፡፡

ይህንን ተከትሎም ክለባችን ያለበትን እዳ ከመክፈሉም በላይ በፊፋ የተጣለበትን የተጫዋቾች ምዝገባ እገዳ የሚነሳለት ይሆናል፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስ የምዝገባ እገዳው ከተነሳለት በኋላ እየተካሄደ ላለው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እና ለሚመጣው የውድድር ዘመን ተጫዋቾችን መመዝገብና ማስፈረም ይችላል፡፡

አቶ ጀማል አህመድና ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ   እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ክለባችን ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚፈልገው ሁሉ የማይተካ ድጋፍ እያደረጉ የቀጠሉ ሲሆን ለክለቡ እድገትና ስኬት እያበረከቱ ላለው የላቀ አስተዋፅኦ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር በክለቡ እና በደጋፊዎቹ ስም የከበረ ምስጋናውን ያቀርባል።

#ይሄነውጊዮርጊሳዊነት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...