ዓለም የደረሰበትን የላቀ የአንሜሽንና ፊልም ሥራ በስፋት መጠቀም ይገባል

Date:

ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ዓለም የደረሰበትን የላቀ የአንሜሽንና ፊልም ሥራ በማስፋፋት ዘመናዊ የፊልም አሠራር ሂደትን ማጠናከር ይገባል አለ፡፡

‘ኢማጂንግ አኒሜሽን ሚዲያ’ የስልጠና ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱን ለማስጀመር የሚያስችል ስምምነትም የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከኮል ጆን ሲ ሮቢንሰን ማዕከል ጋር ተፈራርሟል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ) በስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንዳሉት፤ ስልጠናው የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ አኒሜሽን፣ ሮቦቲክስ፣ የሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ ሲኒማቶግራፊ፣ ዲጂታል አርት፣ የፊልምና ሚዲያ ፕሮዳክሽንን ያካተተ ነው፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎችም፤ የኢትዮጵያን መልክ፣ ታሪክና ባህል ፈጠራ በታከለበት ሁኔታ እንዲገልፁ አቅማቸውን የሚያዳብሩበት ነው ብለዋል፡፡

ዓለም የደረሰበትን የላቀ የአንሜሽንና ፊልም ሥራ በማስፋፋት ዘመናዊ የፊልም አሠራር ሂደትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡

ስልጠናው በአሜሪካዊ የፊልም ባለሙያ ለተከታታይ ሦስት ዓመታት ተከፋፍሎ እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ በዲጂታል ክኅሎት የላቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት እንደሚያስችል ጠቁመዋል፡፡

በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ እና ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ለፕሮጀክቱ ድጋፍ ማድረጋቸውም ተጠቅሷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአሜሪካ ጦር እስራኤልን ከኢራን መከላከሌን ላቆም እችላለሁ አለ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ...

በፌደራሉ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መቀስቀሱ ተገለጸ

ከሱዳን ጋር በሚዋሰነው የሰሜናዊ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል ውስጥ በሚገኝ...

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...