የአሜሪካን ማዕቀብ ፑቲን ማጣጣላቸዉን ተከትሎ የኢኮኖሚ ህመሙ በቅርቡ ይሰማቸዋል ሲሉ ትራምፕ ዛቱ

Date:

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አሜሪካ በሩሲያ ሁለት ትላልቅ የነዳጅ ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ መጣሏን አጣጠጥለዋል፣ ይህንኑ ተከትሎ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንደተናገሩት የሩሲያው ፕሬዝዳንት በቅርቡ የኢኮኖሚውን ህመም እንደሚሰማቸው ጠቁመዋል።

ትራምፕ በዋይት ሀውስ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “እንዲህ አይነት ስሜት ስለሚሰማው ደስተኛ ነኝ” ብለዋል። “ይህ ጥሩ ነው ከስድስት ወር በኋላ ስለ ጉዳዩ አሳውቅዎታለሁ፤  ሁሉም ነገር እንዴት እንደሚሄድ እናያለን” ሲሉ ትራምፕ ተደምጠዋል፡፡

ፑቲን በትላንትናዉ እለት በግዙፎቹ የሩሲያ የነዳጅ ኩባንያዎች በሆኑት በሮስኔፍት እና ሉኮይል ላይ የተጣለውን ማዕቀብ “ወዳጅነት የጎደለው ድርጊት” ሲሉ ገልጸው ነገር ግን ድርጊቱ በሩሲያ ኢኮኖሚ ላይ የሚኖረውን ጉዳት አቅልለውታል።”በተፈጥሯቸው ማዕቀቦች ከባድ ናቸው እናም የተወሰነ ውጤት ይኖራቸዋል፤ ነገር ግን በኢኮኖሚያችን ጤና ላይ ምንም አይነት ተጽእኖ አይኖራቸውም” ሲሉ ፑቲን ተደምጠዋል፡፡

ዩናይትድ ስቴትስ ማዕቀቡን ረቡዕ እለት የጣለችው ሞስኮ በዩክሬን ያለውን ጦርነት ለማቆም የሰላም ሂደት ላይ “ከባድ ቁርጠኝነት ስለሌላት ነው” ማለቷ ይታወሳል፡፡

የግምጃ ቤት ዲፓርትመንት በመግለጫው እንዳስታወቀው እርምጃዎቹ የሩስያን የኢነርጂ ዘርፍ “የክሬምሊን ለጦር መሣሪያዎቿ ገቢ የማሳደግ አቅምን ለመጨመር” እና “የተዳከመ ኢኮኖሚዋን ለመደገፍ” ያነጣጠረዉን እንቅስቃሴ ይጎዳል ብሏል።የግምጃ ቤት ፀሐፊ ስኮት ቤሴንት በመግለጫቸው ላይ “ግድያውን ለማስቆም እና የተኩስ ማቆም እንዲደረስ ጊዜው አሁን ነው” ብለዋል።

#ዳጉ_ጆርናል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...