የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የደኅንነት አዛዡ ማጂድ ኻዴሚ መገደላቸውን በአገሪቱ የዜና ማሠራጫዎች በኩል ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
አብዮታዊ ዘቡ በመግለጫው የደኅንነት አዛዡ ዛሬ ጠዋት መገደላቸውን ገልፆ፤ እስራኤል እና አሜሪካ ማጂድ ኻዴሚን ኢላማ በማድግ ከስሷል።
እስራኤል ደኅንነት አዛዡ ግድያ ኃላፊነቱን ወስዳለች።
የእስራኤል መከላከያ ኃይል በቴሌግራም ላይ ባወጣው የጽሑፍ መልዕክት ግድያውን ለኢራን አብዮታዊ ዘብ “ሌላ ከባድ ኪሳራ” ብሎታል።
ኢራን አብዛኛውን ጊዜ የከፍተኛ ባለሥልጣኖቿን ግድያ ስታረጋግጥ የነበረ እስራኤል እና አሜሪካ ግድያዎቹ መፈጸማቸውን ከገለጹ በኋላ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን የአብዮታዊ ዘቡ አዛዥ ግድያ ቀድማ አሳውቃለች።
ማጂድ ኻዴሚ ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር በተካሄደው የኢራን እና የእስራኤል የ12ቱ ቀናት ጦርነት ወቅት የተገደሉትን ሞሐመድ ካዜሚን ተክተው ሲሠሩ የነበሩ አዛዥ ናቸው።
ማጂድ ኻዴሚ ባለፈው ጥር የተቀሰቀሰውን ኢራን ውስጥ በርካታ ሰዎች የተገደሉበትን ፀረ መንግሥት ተቃውሞ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን በማቀጣጠል ከስሰዋቸው ነበር።
የደኅንነት አዛዡ በተቃውሞው ወቅት የእስራኤል የሳይበር ስለላ ክፍልን ጨምሮ 10 የውጭ አገራት የደኅንነት ተቋማት መላው ኢራንን ባዳራሰው እንቅስቃሴ ውስጥ ተሳትፈዋል ብለዋል።
መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው የሰብዓዊ መብቶች የዜና አገልግሎት በጥር ወሩ የኢራን መንግሥት እርምጃ ቢያንስ 7,000 ሰዎች መገደላቸውን አስታውቋል።
