የአዲስ አበባ የ2019 በጀት 502.27 ቢ. ብር ሆኖ ፀደቀ

Date:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት የሚውል 502 ነጥብ 27 ቢሊየን ብር አጠቃላይ በጀት በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ይህ የዘንድሮው በጀት ከባለፈው ዓመት (2018 ዓ.ም) ጋር ሲነጻጸር የ152 ነጥብ 26 ቢሊዮን ብር (የ43.5%) እጅግ ከፍተኛ ብልጫ አሳይቷል።

ከተመደበው አጠቃላይ በጀት ውስጥ አንበሳውን ድርሻ የያዘው 359 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ለካፒታል ወጪዎች የተመደበ ሲሆን፣ 142 ነጥብ 97 ቢሊየን ብር ለመደበኛ ወጪ እንዲሁም 16 ቢሊየን ብር ለመጠባበቂያ በጀት እንዲሆን ተወስኗል።

ይህ ግዙፍ በጀት በዋናነት የከተማዋን የልማት ስትራቴጂዎች ለማሳካትና የኢኮኖሚ ማረጋጋት ሥራዎችን በመሥራት የኑሮ ውድነትን ለማቃለል ያለመ ነው።

በተጨማሪም ለአዳዲስ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለኮሪደር ልማትና ለተጀመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች ማጠናቀቂያ፣ ለትራንስፖርትና ትራፊክ ፍሰት ማሻሻያ፣ ለቤት ልማት፣ ለውሃ አቅርቦት እና ለመንገድ መሠረተ-ልማት ማስፋፊያ የሚውል ሲሆን፤ የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ብልሹ አሠራርንና ሌብነትን ለመዋጋት በትኩረት እንደሚሠራበት ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...