የአፍሪካ ሴቶች ሰላም እና ደህንነት ኢንስቲትዩት የሴቶችን ሰላም ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ አዉደጥናት በዛሬዉ እለት አካሂዷል።
በመድረኩ ላይም የሚወጡ የህግ ማዕቀፎች እንዳሉ ሆነዉ ተግባራዊነታቸዉ በመላላቱ በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች መበራከታቸዉ ተነስቷል።
ተቋሙ ሴቶች በተለያዩ መድረኮች ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ እና ባሉበት ሁሉ ሰላማቸዉ ሊጠበቅ እንደሚገባ አሳስቧል።
በመድረኩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለሰላም ግንባታ ያላቸው ሚና እና የሴቶች የሰላም ግንባታ እና የፖሊሲ ማዕቀፎች ላይ ያተኮሩ እና ሌሎችም ጥናቶች ቀርበዋል።
