የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት የሚዲያ ባለሙያዎችን የመመዝገብም ሆነየሙያ ማረጋገጫ የመስጠት ተግባርና ኃላፊነት አልተሰጠውም ተባለ

Date:

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት፣ ለጋዜጠኞች የሙያ ማረጋገጫ ለመስጠትና የጋዜጠኞች ምዝገባ ለማከናወን ውይይትና እንቅስቃሴ መጀመሩን ተከትሎ፤ የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት፣ ጋዜጠኞችና የሙያ ማህበራት ጉዳዩን በተመለከተ የሕጋዊነት ጥያቄና ስጋቶቻቸውን በማቅረብ ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አስታውቋል።

ባለሥልጣኑ ባወጣው መግለጫ፤ የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ጋዜጠኞችን ወይም የሚዲያ ባለሙያዎችን የመመዝገብም ሆነ የሙያ ማረጋገጫ የመስጠት ተግባርና ኃላፊነት በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አልተሰጠውም ብሏል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን፣ ለዚህ የምክር ቤቱ ተግባር እውቅና እንደማይሰጥ አስታውቋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...