የጃፓኑ የፀሐይ ኃይል አምራች በኢትዮጵያ የማምረት አቅሙን  ወደ 4 ጊጋ ዋት ለማሳደግ አቀደ

Date:

የጃፓን የፀሐይ ኃይል አምራች ኩባንያ የሆነው ቶዮ ሶላር፤ በኢትዮጵያ ያለውን ዓመታዊ የሶላር ሃይል የማምረት አቅሙን ከ 2 ጊጋዋት ወደ 4 ጊጋዋት በእጥፍ ለማሳደግ ማቀዱን አስታወቀ።

ኩባንያው በየካቲት ወር የሙከራ ምርቱን በጀመረበት እና ፋብሪካው በሚገኝበት የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ሁለተኛ የማምረቻ ፋብሪካውን ለመከራየት ማሰቡን አመልክቷል።

የአዲሱ ፋብሪካ ግንባታ በሚያዝያ ወር ይጀመራል የተባለ ሲሆን ሥራውን በነሐሴ ወር በይፋ እንደሚጀምር ተመላክቷል።

የመጀመሪያው ፋብሪካ ኢንቨስትመንት 60 ሚሊዮን ዶላር  የፈጀ ሲሆን ለሁለተኛው ፋብሪካ 47 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ተብሏል።

ኩባንያው ምርት ከጀመረበት ከጎርጎሮሳውያኑ ጥቅምት 2023 ጀምሮ 1.3 ጊጋዋት የሶላር ሴሎችን ወደ ውጭ መላኩ ተጠቁሟል።

በኢትዮጵያ የተመረቱት ሴሎቹ በአሜሪካ ወደሚገኘው ሞጁል ማምረቻ ፋብሪካ የሚላኩ ሲሆን፣ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2026 መጀመሪያ ድረስ በአሜሪካ የተለየ “የሶላር ሴል ማምረቻ ፋብሪካ” ለመገንባትም አቅዷል።

የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ጁንሴይ ሪዩ “የመጀመሪያው ምዕራፍ ሙሉ በሙሉ ከመጠናቀቁ በፊት ለሶላር ሴል ምርቶቻችን ያገኘነው ዓለም አቀፋዊ ፍላጎት እና ትዕዛዞች የስትራቴጂካዊ ራዕይ ጥንካሬን ያረጋግጣሉ” ብለዋል።

አክለውም “ዓለም አቀፋዊ ፍላጎትን ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህንን ተጨማሪ አቅም ለማሳደግ ወስነናል” ሲሉ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ብቻ ከ12ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አሉ

በሱዳን የሚገኘው የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ...

ትራምፕ አሜሪካ እና ኢራን “በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ” ሊወያዩ እንደሚችሉ ተናገሩ

ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል “በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት...

የኢራን ጦርነት የሚቀጥል ከሆነ የዓለም ምጣኔ ኃብት አደጋ ላይ እንደሚወድቅ አይኤምኤፍ አስጠነቀቀ

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በመካከለኛው ምሥራቅ የሚካሄደው የኢራን...

የመምህር ዘላለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የ፵ ቀን መታሰቢያ ጥሪ

​"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው!" (ምሳሌ ፲፥፯)​በሕይወትና በቃል ትምህርታቸው ብዙዎችን...