ትራምፕ አሜሪካ እና ኢራን “በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ” ሊወያዩ እንደሚችሉ ተናገሩ

Date:

ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል “በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ” ንግግር ሊጀመር እንደሚችል ለኒውዮርክ ፖስት ተናገሩ።

“በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ የሆነ ነገር ሊከሰት ይችላል። እና እኛ የበለጠ ወደዚያ [ፓኪስታን] የመሄድ ዝንባሌ አለን” ማለታቸውን ጋዜጣው ዘግቧል።

ሁለቱ አገራት የተኩስ አቁም ከደረሱ በኋላ በፓኪስታን ተገናኝተው ለረዥም ሰዓት የተወያዩት ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ነበር።

በወቅቱ የአሜሪካን ልዑክ የመሩት ምክትል ፕሬዜዳንቱ ጄዲ ቫንስ ሲሆኑ የኢራን ልዑክ ደግሞ የተመራው በአፈ ጉባዔ ሞሐመድ ባገር ጋሊባፍ ነበር።ነገር ግን ውይይቱ ያለምንም ስምምነት ተቋጭቷል።

ዛሬ የኢራን መገናኛ ብዙኃን በፓኪስታን እና ቴህራን መካከል የመልዕክተት ልውውጥ መኖሩን ዘግበው ከአሜሪካ ጋር ቀጣይ ውይይት ለማድረግ ስምምነት ስለመደረሱ ግን “ምንም መረጃ የለም” ብለው ነበር።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...