የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ኢትዮጵያ መድን ከ40 ሚሊየን ብር በላይ አገኘ

Date:

ኢትዮጵያ ቡና ከ37 ሚ ብር በላይ፣ ባህርዳር ከተማ ከ35 ሚ. ብር በላይ አግኝተዋል

የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው የኢትዮጵያ መድን ከ40 ሚሊየን ብር በላይ አግኝቷል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር፣ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ከብሮድካስትና ስም ስያሜ መብት የሚያገኙትን ክፍፍል ይፋ አድርጓል።

በዚህም ዓመቱን በአሸናፊነት ያጠናቀቀው ኢትዮጵያ መድን፣ 40 ሚሊየን 295 ሺህ ብር በላይ ማግኘቱ ተገልጿል።

በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው ኢትዮጵያ ቡና፣ 37 ሚሊየን 703 ሺህ ብር ያገኘ ሌላኛው ክለብ እንደሆነ ተመላክቷል።

በተጨማሪም ባሕር ዳር ከተማ 35 ሚሊየን 281 ሺህ 37 ብር ማግኘቱን የገለጸው አክሲዮን ማህበሩ፤ በአጠቃላይ በ2017 የፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ለሆኑ ክለቦች 428 ሚሊየን 846 ሺህ ብር ማከፋፈሉን አስታውቋል፡፡

(WMCC)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...