ኢትዮጵያ ቡና ከ37 ሚ ብር በላይ፣ ባህርዳር ከተማ ከ35 ሚ. ብር በላይ አግኝተዋል
የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው የኢትዮጵያ መድን ከ40 ሚሊየን ብር በላይ አግኝቷል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር፣ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ከብሮድካስትና ስም ስያሜ መብት የሚያገኙትን ክፍፍል ይፋ አድርጓል።
በዚህም ዓመቱን በአሸናፊነት ያጠናቀቀው ኢትዮጵያ መድን፣ 40 ሚሊየን 295 ሺህ ብር በላይ ማግኘቱ ተገልጿል።
በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው ኢትዮጵያ ቡና፣ 37 ሚሊየን 703 ሺህ ብር ያገኘ ሌላኛው ክለብ እንደሆነ ተመላክቷል።
በተጨማሪም ባሕር ዳር ከተማ 35 ሚሊየን 281 ሺህ 37 ብር ማግኘቱን የገለጸው አክሲዮን ማህበሩ፤ በአጠቃላይ በ2017 የፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ለሆኑ ክለቦች 428 ሚሊየን 846 ሺህ ብር ማከፋፈሉን አስታውቋል፡፡
(WMCC)
