ፌዴራል ፖሊስ ከተባበሩት መንግሥታት የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን በድጋፍ አገኘ

Date:

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ ከተባበሩት መንግሥታት የሴፍቲና የሴኩሪቲ ዲፓርትመንት ለወንጀል መከላከል ሥራ አጋዥ የሆኑ ዘመናዊ ኮምፒውተሮችንና የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን በድጋፍ ማግኘቱን አስታወቀ።

ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በተከናወነው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት፣ የዲፓርትመንቱ ኃላፊ ሚስተር ፕሪንስ ብሩስ መሣሪያዎቹን ለፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ አስረክበዋል።

ምክትል ኮሚሽነሩ በዚሁ ወቅት በድጋፍ የተገኙት ቁሳቁሶች ተቋሙ እያከናወነ ላለው የወንጀል መከላከል ተግባር ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖራቸው ገልፀዋል።

የዲፓርትመንቱ ኃላፊ ሚስተር ፕሪንስ ብሩስ በበኩላቸው፤ ተቋማቸው ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ድጋፍ በማድረጉ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው፣ በቀጣይም በወንጀል መከላከል ዙሪያ በትብብር ለመሥራትና ሌሎች መሰል ድጋፎች እንደሚደረጉ መናገራቸውን ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...