ቀይ መስቀል ማኅበር የተደራሽነት ችግር ገጠመዉ

Date:

በሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ ከመኖሪያ ቀዬአቸው ለተፈናቀሉ እንዲሁም የሰብዓዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ነዋሪዎች ድጋፍ ለማድረግ የአባላት ቁጥር ዝቀተኛ መሆንና የፋይናንስ ችግር ተግዳሮት እየሆነበት እንደሚገኝ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ለአሐዱ አስታውቋል።

በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በሚባል ደረጃ ቀይ መስቀል ማኅበርን ‘በውጭ ድጋፍ የሚንቀሳቀስ የተራድኦ ድርጅት አድርጎ የማሰብ የተሳሳተ አመለካከት አለ’ የተባለ ሲሆን አባል የመሆን እና የአባልነት ክፍያ የመፈጸም ተነሳሽነት አለመኖሩም ተነግሯል።

በቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የሰብዓዊ ዲፕሎማሲና ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዳይሬክተር ሙሉዋስ አቲሳ በክልሉ 10 ሚሊዮን ገደማ የሚገመት ነዋሪ ቢኖረም የቀይ መስቀል አባላት ቁጥር ከ80 በመቶ በታች መሆኑን ለአሐዱ አብራርተዋል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከአባላት በሚገኝ መዋጮ እና ከሌሎች ምንጮች በሚያገኘው ገቢ የሚተዳደር መሆኑን አውቆ ሁሉም ማኅበረሰብ አባል በመሆን እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

(አሐዱ ሬድዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...