ቀይ መስቀል ማኅበር የተደራሽነት ችግር ገጠመዉ

Date:

በሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ ከመኖሪያ ቀዬአቸው ለተፈናቀሉ እንዲሁም የሰብዓዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ነዋሪዎች ድጋፍ ለማድረግ የአባላት ቁጥር ዝቀተኛ መሆንና የፋይናንስ ችግር ተግዳሮት እየሆነበት እንደሚገኝ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ለአሐዱ አስታውቋል።

በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በሚባል ደረጃ ቀይ መስቀል ማኅበርን ‘በውጭ ድጋፍ የሚንቀሳቀስ የተራድኦ ድርጅት አድርጎ የማሰብ የተሳሳተ አመለካከት አለ’ የተባለ ሲሆን አባል የመሆን እና የአባልነት ክፍያ የመፈጸም ተነሳሽነት አለመኖሩም ተነግሯል።

በቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የሰብዓዊ ዲፕሎማሲና ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዳይሬክተር ሙሉዋስ አቲሳ በክልሉ 10 ሚሊዮን ገደማ የሚገመት ነዋሪ ቢኖረም የቀይ መስቀል አባላት ቁጥር ከ80 በመቶ በታች መሆኑን ለአሐዱ አብራርተዋል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከአባላት በሚገኝ መዋጮ እና ከሌሎች ምንጮች በሚያገኘው ገቢ የሚተዳደር መሆኑን አውቆ ሁሉም ማኅበረሰብ አባል በመሆን እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

(አሐዱ ሬድዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...