በከተሞች ያለውን የቤት ፍላጎት ለማሟላት 80 በመቶ በግል ባለሀብቶች  እንዲሸፈን ታቀደ

Date:

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በከተሞች ባለው የቤት ግንባታ ላይ የመንግስት ድርሻ 20 በመቶ እንደሚሆን ገልጿል።

በሚኒስትሮች ምክር ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የቤቶች ፓሊሲ መጽደቁን ለአሐዱ የገለጹት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ናቸው።

ሁሉንም ሰው የቤት ባለቤት ማድረግ አይቻልም ያሉት ወ/ሮ ጫልቱ የቤቶች ፓሊሲውን ተከትለው በሚወጡ መመሪያዎች መንግስት 20 በመቶውን ለአቅመ ደካሞች እና ለሀገር ባለውለታዎች ቤት እንዲሰራ የሚያደርጉ ናቸው ብለዋል።

የተቀረውን 80 በመቶ መንግስት ምቹ ምህዳርን እየፈጠረ የግል ባለሀብቱ እንዲሳተፍ  በማድረግ   አቅም ያለው የቤት ባለቤት እንዲሆን አልያም በገቢው ልክ የኪራይ አማራጭን እንዲያገኝ ማድረግ መሆኑን ለአሐዱ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም የቤት ፓሊሲ እንደሀገር አለመኖሩን አስታውሰው በመንግስት በከተሞች ይሰራ የነበረው የጋራ መኖሪያ ቤት (ኮንዶሚንየም ) መንግስት በስፋት የተሳተፈበት መሆኑና የፕሮጀክት አፈጻጸሙ መዘግየትን ጨምሮ ትክክል ያልሆኑ አሰራሮች እንደነበሩም ገልጸዋል፡፡

የጋራ መኖሪያ ቤት አቅም የሌላቸው ዜጎችን ለይቶ ለመጥቀም የታሰበ ቢሆንም ከምዝገባ ስርዓቱ አንስቶ በነበረው ልክ ያልሆነ አሰራር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት “ላለው የሚጨምር እንጂ ቤት የሌላቸው ዜጎችን ለይቶ ችግራቸውን የሚፈታ እንዳልነበር  ሲሉ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

(አሐዱ ራድዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...