በጋዛ የሃማስ መሪ የሆነው መሀመድ ሲንዋር መገደሉን እስራኤል አስታወቀች

Date:

የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፥ በእስራኤል በጥብቅ ከሚፈለጉት የሃማስ ሰዎች መካከል አንዱ እና በጋዛ የሃማስ መሪ የሆነው መሃመድ ሲንዋር በጦራቸውመገደሉን ገልጸዋል።

መሀመድ ሲንዋር ባሳለፍነው ግንቦት 5  ቀን በደቡባዊ ካን ዮኒስ የአውሮፓ ሆስፒታል ግቢ እና አካባቢ ላይ የተደረገው የእስራኤል ከፍተኛ ጥቃት ዒላማ መሆኑ ተገልጿል። የእስራኤል ወታደራዊ ሃይል የሃማስን የምድር ውስጥ የጉዞ መስመር እና የተለያዩ ቢሮዎች በጥቃቱ ማውደም እንደቻለ በወቅቱ ገልጾ ነበር።

በጋዛ ሃማስ የሚመራ የሲቪል መከላከያ ኤጀንሲ በጥቃቱ 28 ሰዎች መሞታቸውን ቢገልጽም ከሲንዋርን ጋር በተያያዘ በህወት ይኑር ወይም ይሙት ምንም አይነት መረጃን አላወጣም።

እ.ኤ.አ ጥቅምት 7/ 2023 በእስራኤል ላይ የተፈፀመው ጥቃት ዋና አቀነባባሪ የተባለው እና የመሀመድ ሲንዋር ወንድም የሆነው ያህያ ሲንዋር ባለፈው ጥቅምት ወር በእስራኤል ወታደሮች መገደሉ ይታወሳል ሲል የዘገብው ቢቢሲ ነው።

የእስራኤል እና ሃማስ ግጭት ለ20 ወራት የዘለቀ ሲሆን፤ በተለያየ ጊዜ የተኩስ አቁም ስምምነቶች ቢደረጉም እስካሁን ዘላቂ መፍትሄ ሊበጅለት አልቻለም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...