በጋዛ የሃማስ መሪ የሆነው መሀመድ ሲንዋር መገደሉን እስራኤል አስታወቀች

Date:

የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፥ በእስራኤል በጥብቅ ከሚፈለጉት የሃማስ ሰዎች መካከል አንዱ እና በጋዛ የሃማስ መሪ የሆነው መሃመድ ሲንዋር በጦራቸውመገደሉን ገልጸዋል።

መሀመድ ሲንዋር ባሳለፍነው ግንቦት 5  ቀን በደቡባዊ ካን ዮኒስ የአውሮፓ ሆስፒታል ግቢ እና አካባቢ ላይ የተደረገው የእስራኤል ከፍተኛ ጥቃት ዒላማ መሆኑ ተገልጿል። የእስራኤል ወታደራዊ ሃይል የሃማስን የምድር ውስጥ የጉዞ መስመር እና የተለያዩ ቢሮዎች በጥቃቱ ማውደም እንደቻለ በወቅቱ ገልጾ ነበር።

በጋዛ ሃማስ የሚመራ የሲቪል መከላከያ ኤጀንሲ በጥቃቱ 28 ሰዎች መሞታቸውን ቢገልጽም ከሲንዋርን ጋር በተያያዘ በህወት ይኑር ወይም ይሙት ምንም አይነት መረጃን አላወጣም።

እ.ኤ.አ ጥቅምት 7/ 2023 በእስራኤል ላይ የተፈፀመው ጥቃት ዋና አቀነባባሪ የተባለው እና የመሀመድ ሲንዋር ወንድም የሆነው ያህያ ሲንዋር ባለፈው ጥቅምት ወር በእስራኤል ወታደሮች መገደሉ ይታወሳል ሲል የዘገብው ቢቢሲ ነው።

የእስራኤል እና ሃማስ ግጭት ለ20 ወራት የዘለቀ ሲሆን፤ በተለያየ ጊዜ የተኩስ አቁም ስምምነቶች ቢደረጉም እስካሁን ዘላቂ መፍትሄ ሊበጅለት አልቻለም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚገኙ ዜጎቿ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ አስተላለፈች

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ አዳዲስ ወታደራዊ ጥቃቶች ሊሰነዘሩ...

ፍትህ ተሰውቶ የጉልበት ብልጫ የገነነበት ውሳኔ ነው

ለኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች የክፍያ ስርዓት መመሪያ (Financial...

“ተፅዕኖ ፈጣሪዎች” የተባሉ ግለሰቦች በምክክሩ እንዲሳተፉ በምን መስፈረት ተመረጡ?

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 17ኛ ቀን ውሎ የክልል ተወካዮች ጉባኤ...

የአሜሪካ ጦር እስራኤልን ከኢራን መከላከሌን ላቆም እችላለሁ አለ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ...