የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግለት የ700 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ዘርፍ ማጠናከሪያ ፕሮጀክት መጀመሩን ያሳወቀ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ የመጀመሪያው የ250 ሚሊዮን ዶላር ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተላልፏል።
ይህ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የፋይናንስ ፎረም ላይ ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ በብሔራዊ ባንክ፣ በንግድ ባንክ እና በልማት ባንክ የሚተገበር ነው። ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ይበልጥ ጠንካራና ዘላቂ የፋይናንስ ዘርፍ ለመገንባት በምታደርገው ጉዞ ላይ ትልቅ እርምጃ እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ ወሳኝ ተነሳሽነት የፋይናንስ ዘርፉን መረጋጋት በማሳደግ ለረዥም ጊዜ ልማት ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሏል።
