የአርሰናል ሴቶች ቡድን የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታውን ከባርሴሎና ጋር አድርጎ 1ለ0 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነዋል።
አርሰናል በታሪኩ ለሁለተኛ ጊዜ የሴቶች የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫውን ማሸነፍ ችሏል።
የሀገር ውስጥ ሶስትዮሽ ዋንጫ አሸናፊው ባርሴሎና ከተከታታይ ሶስት አመታት የውድድሩ አሸናፊነት በኋላ ዋንጫውን አጥተዋል።
የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ያሸነፈ ብቸኛው የእንግሊዝ ቡድን የሆነው አርሰናል ሪከርዱን በሌላ ዋንጫ አሻሽሎታል።
የአርሰናል ዋና አሰልጣኝ ሬኔ ሴሌገርስ የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ያሸነፈች በታሪክ የመጀመሪያዋ ኔዘርላንዳዊት አሰልጣኝ መሆን ችላለች።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
