ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን “ለነዳጅ እና ጋዝ ላኪዎች ሙሉ በሙሉ ለመዝጋት” ዛተች

Date:

በኢራን እና በአሜሪካ መካከል የተኩስ ልውውጥ መደረጉን ተከትሎ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የሆርሙዝ ወሽመጥን “ለነዳጅ እና ጋዝ ላኪዎች ሙሉ በሙሉ ለመዝጋት” ዛተ።

በባሕረ ሰላጤው አካባቢ ሁለቱ አገራት የተኩስ ልውውጥ ካደረጉ በኋላ እስላማዊ አብዮታዊ ዘቡ በሰጠው ማስጠንቀቂያ የሆርሙዝ ወሽመጥ ለነዳጅ እና ለጋዝ ላኪዎች ሙሉ በሙሉ ቢዘጋ “ኃላፊነቱን የምትወስደው አሜሪካ ናት” ብሏል።

አሜሪካ “እኩይ ድርጊቷን ከቀጠለች” ለሚወስደው እርምጃ ኃላፊነቱን እንደምትወስድም አስታውቋል።

የአሜሪካ ጦር ኢራን ወደ ሆርሙዝ ወሽመጥ የተኮሰቻቸውን አራት ድሮኖች መትቶ መጣሉን አስታውቋል።

የአሜሪካ ጦር ማዕከላዊ ዕዝ፤ ጎሩክ እና ቃሽም በተባሉ ደሴቶች ላይ የኢራን የባሕር ዳርቻ ጥበቃ ማዕከላት ላይ ጥቃት መፈጸሙን ገልጿል።

ኢራንም በአጸፋው በኩዌት የሚገኙ ሁለት የአሜሪካ ጦር መቀመጫዎች ላይ ባለስቲክ ሚሳዔል ተኩሳለች። በባሕሬን በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይም ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።

የባሕሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢራን ያደረሰችውን ጥቃት “በጽኑ” እንደሚያወግዝ አስታውቋል። በባሕሬን እንዲሁም በኩዌት ላይ የደረሰውን ጥቃት “ግልጽ ጸብ አጫሪነት” ብሎታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...