ኢትዮጵያ ያለው የሎጅስቲክስ ዘርፍ እጅግ በጣም ዝቅተኛና ኋላቀር መሆኑ ተገለጸ

Date:

ኢትዮጵያ የራሷ የባህር ወደብ የሌላት መሆኑ የሎጅስቲክሱ ዘርፍ እጅግ በጣም ዝቅተኛና ኋላቀር ካደረጉት ምክንያቶች ውስጥ አንዱ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ፍሬት ፎርዋርደርስ ኤንድ ሺፒንግ ኤጀንትስ አሶሴሽን ከብሪታኒያ ዓለም አቀፍ የጭነት አስተላላፊዎች ማኅበር ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ በተፈራረሙበት ወቅት ነው፡፡

ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል በተካሄደ ሥነ ሥርዓት ላይ በኢትዮጵያ ያለው የሎጅስቲክስ ዘርፍ ከዓለም ሁኔታ አንጻር ሲወዳደር እጅግ በጣም ዝቅተኛና ኋላቀር መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ የጋራ መግባቢያ ሰነዱ መ’ፈረሙ የኢትዮጵያን የሎጅስቲክስ ዘርፍ ዘመናዊና ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችል እርምጃ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡

ከተቀረው ዓለም ጋር ሲወዳደር እጅግ በጣም ዝቅተኛና ኋላቀር ነው ለተባለው የኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ ዘርፍ ከባህር ወደብ አለመኖር በተጨማሪ በቂና ዘመናዊ የመሠረተ ልማት አውታሮች አለመኖራቸው፣ ለዘርፉ የሚመጥን የተቀናጀ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አለመኖሩ፣ እንዲሁም በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረትና ሌሎችም አበይት ምክንያቶች ናቸው ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ፍሬት ፎርዋርደርስ ኤንድ ሺፒንግ ኤጀንትስ አሶሴሽን ከብሪታኒያ ዓለም አቀፍ የጭነት አስተላላፊዎች ማኅበር ጋር የተፈራረመው ስምምነት የሎጅስቲክስ ዘርፉን ለማዘመን ከፍተኛ አገራዊ ፋይዳ እንዳለውም በመድረኩ ተገልጿል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...