አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የሚያካሂዱትን ጥቃት ከጀመሩበት ደቂቃ አንስቶ እስካሁን ድረስ ዋነኛ ዒላማ እያደረጓቸው ያሉት የአገሪቱን ከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ መሪዎችን ነው።
በመጀመሪያው ቀን ጥቃት የአገሪቱ ጠቅላይ መሪ የሆኑት አያቶላህ አሊ ኻሜኒን ጨምሮ ሌሎች ቁልፍ ባለሥልጣናት በጽህፈት ቤታቸው እና በመኖሪያቸው ላይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ተገድለዋል።
በአገሪቱ ውስጥ በተለያዩ የሥልጣን ደረጃ ላይ የሚገኙ በርካታ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ባለሥልጣናት ባለፉት ዓመታት ጭምር ተገድለዋል። አሁን የተከፈተው ጦርነት ደግሞ ሌሎቹንም የጥቃት ዒላማ አድርጓቸዋል።
ለመሆኑ ወሳኝ ከሚባሉት ሰባት የኢራን ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ መሪዎች መካከል በአሁኑ ወቅት ከጥቃት ተርፈው በሕይወት የሚገኙት ፕሬዝዳንቱ መሱድ ፔዜሽኪያን ብቻ ናቸዉ።
