አጭበርባሪዎች ከባንክ የተደወለ በማስመሰል ‘የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎትዎን እናስተካክልልዎት፣ ሽልማት ደርሶዎታል፣ የፋይዳ መታወቂያዎን ከሂሳብዎ ጋር እናስተሳስርልዎ’ የሚሉ እና ሌሎች ማሳሳቻ መልዕክቶችን በመጠቀም ከደንበኞች ሂሳብ ላይ ስርቆት ለመፈፀም ይሞክራሉ፡፡
በመሆኑም ከባንክ ነው በሚል የሚደርስዎትን ጥሪ ትክክለኛነት ወደ ቅርንጫፍ በመሄድ አሊያም ወደ 951 በመደወል ሳያረጋግጡ ምንም አይነት እርምጃ እንዳይወስዱ፣ የባንክ መረጃዎንም በስልክ እንዳይሰጡ እናሳውቃለን፡፡
በተጨማሪም ከአጭበርባሪዎች ጥሪ ሲደርስዎት የተደወለበትን ስልክ ቁጥር በ951 እንዲያስመዘግቡ በአክብሮት እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
