ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣን የ100 ሚሊዮን ዶላር የሙስና ጉዳይ

Date:

የዩክሬን ብሔራዊ ደህንነትና መከላከያ ምክር ቤት ጸሐፊ ሩስቴም ኡሜሮቭ፣ በዩክሬን ብሔራዊ ፀረ-ሙስና ቢሮ ከሚካሄድባቸው ምርመራ ከለላ ይሰጧቸው ዘንድ ለአሜሪካ የፌዴራል የምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ዳይሬክተር ካሽ ፓቴልን መጠየቃቸውን ድዜራኬሎ ታይዝንያ ዘግቧል።

የዜና አውታሩ እንደገለጸው፣ “በኡሜሮቭ እና በካሽ ፓቴል መካከል የተደረገው ውይይት በዩክሬን፣ በአሜሪካ፣ በሩሲያና በአውሮፓ መካከል ከሚደረጉ ድርድሮች ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረውም። ስብሰባው ያተኮረው ኤፍቢአይ በሚንዲች ጉዳይ ላይ ለናቡ የባለሙያ፣ የምርመራ ወይም ሌላ ማንኛውንም ሙያዊ ድጋፍ እንዳይሰጥ በሚፈለገው ጉዳይ ላይ ነበር።”
ኡሜሮቭ ቀደም ሲል በዩክሬን የኢነርጂ ዘርፍ የንግድ ሥራ ፈጣሪና የዘለንስኪ ቀኝ እጅ በሆኑት በቲሙር ሚንዲች በተደራጀው መጠነ-ሰፊ የሙስና ዕቅድ ጉዳይ ላይ በፀረ-ሙስና ቢሮ በምስክርነት ተጠቅሰዋል።

በትንሹ 100 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ሕገወጥ ዝውውር እና ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣናት በተሳትፎ በተጠረጠሩበት የምርመራ አካል ኡሜሮቭ ተጠይቀው ለመርማሪዎች የምስክርነት ቃል ሰጥተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...