የገንዘብ ሚኒስቴር ከ30 ሺህ ብር በላይ የጥሬ ገንዘብ ግብይት ላይ እገዳ የሚጥለውን የሕግ ማሻሻያ ለፓርላማ አቀረበ፡፡
ገደቡን ያለፈ ማንኛውም ግብይት በሞባይል ገንዘብ ማስተላለፊያና ፍቃድ የተሰጣቸው የፋይናንስ ተቋማትን ጨምሮ በመደበኛ የባንክ ሂደት እንዲፈፀም ይገደዳል ተብሏል።
ሚኒስቴሩ እርምጃው የመንግሥት አስተዳደርን ለማዘመንና የግብር አሰባሰብን ለማሻሻል ወሳኝ ነው ብሏል፡፡
በአንድ ቀን ውስጥ የሚደረግ የተከፋፈለ ክፍያ እንደ ነጠላ ግብይት የሚቆጠር ሲሆን፤ ገደቡን የተላለፈ ሰው የተቀበለውን ክፍያ እጥፍ ሊቀጣ እንደሚችልና ወጪው ከግብር ቅነሳ ውጪ እንደሚሆን በረቂቅ ሕጉ ተቀምጧል፡፡
sputnik
