‌‎የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላለፈ

Date:



‎ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል ቅዳሜ ይከበራል።

በዓሉን አስታኮ ግን አንዳንድ አገልግሎት ሰጪዎች ከፍ ያለ የዋጋ ጭማሪ እያደረጉ እንደሆነ በግልጽ ታይተዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያም  ” ጥቂት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በዓሉን አስታከው በአንዳንድ አገልግሎቶችና በማረፊያ ቦታዎች ላይ ከወትሮው ውጭ የዋጋ ጭማሬ የሚመስሉ አዝማሚያዎችን እያደረጉ ስለመገኘታቸው ጥቆማዎች ቀርበውልኛል ” ብሏል።

” የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በእነዚህ አብዛኛው አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በማይወክሉ ላይ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ቀደም ብለው እንዲታረሙ በጥብቅ ያሳስባል ” ሲል ገልጿል።

” ‎ይህ አይነቱ ድርጊት በተለይም ሁላችንም የአይን ብሌን አድርገን የምናያትን ከተማችን የሀዋሳን ስም የሚያጠለሽ ሆኖ እንዳይገኝ ከወዲሁ በመሰል ድርጊት ላይ የተሰማሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ማስገንዘብ እንወዳለን ” ሲል መምሪያው አሳስቧል።

” ‎በጥቆማው መሰረት በተጨባጭ መልኩ በዓሉን አስታከው ያልተገባ የዋጋ ጭማሬ በማንኛውም አገልግሎት ላይ በሚያደርጉ አካላት ላይ አስተዳደሩ የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል ” ብሏል።

@tikvahethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...