የመምህራን ደሞዝ በጊዜ አለመከፈል ለተማሪዎች ውጤት ማሽቆልቆል መንስኤ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ያስጠናው ጥናት አመላከተ
በአንዳንድ አካባቢዎች መምህራን ስላልተደገፉና የሦስት ወር ደሞዝ ያልተከፈላቸው በመሆኑ ለተማሪዎች ውጤት ማሽቆልቆል አንዱ ምክንያት መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ያስጠናው ጥናት አመላከተ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ፕሮግራሞችና መሻሻል መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዮሃንስ ወጋሶ የጥናት ውጤት አስመልክተው እንደገለጹት በአንዳንድ አካባቢዎች መምህራን ወደ ክፍል አለመግባት፣ በፍላጎት አለማስተማር እና የሦስት ወር ደሞዝ ያልተከፈላቸው አስተማሪዎች መኖር ለተማሪዎች ውጤት መቀነስ በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡
የተማሪዎች ለፈተና ከቦታ ቦታ መጓጓዝና ምቹ ባልሆነ ሁኔታ መቅረብ በውጤት ላይ አሉታዊ ሚና እንዳለው የጋዜጣ_ፕላስ ዘገባ ያሳያል ፡፡
