የሶስት ወራት ቁጥሮች ምን ይነግሩናል ?

Date:

▶️ ባለፉት ሶስት ወራት የተሰበሰበው የፌደራል መንግስት ገቢ 323 ቢሊየን ብር ደርሷል፤

▶️ ይህ አፈጻጸም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ112 በመቶ ጭማሪ ያለው ሲሆን ÷ በወቅቱ የተሰበሰበው ገቢ 152 ቢሊየን ብር ነበር፡፡

▶️ ባለፉት ሶስት ወራት ከወርቅ 1 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር  ገቢ ተገኝቷል፤

▶️ ከቡና ደግሞ 763 ሚሊየን ዶላር ተገኝቷል 

▶️ ባለፉት 100 ቀናት ከአጠቃላይ የውጭ ምንዛሪ 8.29 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል ፤

▶️ ከወጪ ንግድ የሚመጣው የውጭ ምንዛሪ 57.6 በመቶ ደርሷል።

▶️ ባንኮች ባለፉት ሦስት ወራት እርስ በርሳቸው 19.2 ሚሊዮን ዶላር ሲያገበያይ፤ ብሔራዊ ባንክ ደግሞ 150 ሚሊዮን ዶላር አጫርቷል።

▶️ የሃዋላ ፍሰት 2 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን፤

▶️ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ደግሞ 961 ሚሊየን ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

▶️ አጠቃላይ ተቀማጭ ሃብት 3 ነጥብ 73 ትሪሊየን ብር ደርሷል ፤

▶️  በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገር የሥራ ስምሪት ለ671 ሺህ 589 ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡

▶️ በዚህ መሰረትም በሀገር ውስጥ ለ535 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን፤

▶️ ከዘርፍ አንጻርም

❇️ በግብርና ለ186 ሺህ ፣

❇️ በኢንዱስትሪ ለ122 ሺህ እንዲሁም

❇️ በአገልግሎት ለ227 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።

▶️ በተመሳሳይ በውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት ለ136 ሺህ 589 ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፤

▶️ በተኪ ምርትም ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል

▶️ ባለፉት ሦስት ወራት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ በ13 በመቶ በማደግ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እድገቱን እየመራ ነው፤

▶️ በመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት በጠቅላላ 132 አዳዲስ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ ገብተዋል።

▶️ ለግሉ ዘርፍ እና ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች የሚደረገው የፋይናንስ ድጋፍ ከፍ ማለቱ በዘርፉ ላይ ትልቅ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ተመላክቷል።

▶️ በሌላ በኩል ባለፉት ሶስት ወራት በግብርናው ዘርፍ ውጤታማ ሥራ መከናወኑ ተሰርቷል፤

▶️ በዘርፉ በአጠቃላይ 242 ሚሊየን ኩንታል ምርት የተሰበሰበ ሲሆን ፥ ከዚህ ውስጥ 74 ነጥብ 73 በመቶው የሰብል ምርት ነው ፤

▶️ 2.45 ሚሊዮን ሔክታር መሬት ላይ የሆርቲካልቸር ምርቶች እየለሙ ነው።

▶️ የሆርቲካልቸር ዘርፉ ልማት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፃር የ31.7 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፤

▶️ ባለፉት መቶ ቀናት 376 ሺህ 615 የውጭ ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል፤

▶️ 29 ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶችን ማዘጋጀት ተችሏል፤

▶️ በእነዚህ ኮንፈረንሶች ላይም 35 ሺህ 115 የውጭ ሀገር ዜጎች ተሳትፈዋል፤

የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በመንገድ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ

አደጋው የደረሰው ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ...

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...