የነዳጅ ምርትን ለመቆጠብ ማህበረሰቡ በእግር እና የብስክሌት አማራጮችን እንዲጠቀም ጥሪ ቀረበ

Date:


በመካከለኛው ምስራቅ የተፈጠረው ቀውስ ተፅዕኖ ተከትሎ በሀገራችንና በዓለም ላይ ነዳጅን በገበያ ላይ ለማግኘት አስቸጋሪ እየሆነ መመምጣቱን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስትር ዴዔታው በርሆ ሀሰን ለኤን ቢሲ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቀውሱ ኢትዮጵያ ነዳጅ በምታጓጉዝበት የባህር ኃይል መስመር ላይ ከፍተኛ የጥቃት ተጋላጭነት እየጨመረ መጥቷል ብለዋል።

ሚኒስትር ዴታው የተፈጠረውን ወቅታዊ የነዳጅ እጥረት ተቋቁሞ ችግሩን ለመሻገር ተቋማት ማህበረሰቡ እና ለተሽከርካሪ አስመጪዎች አማራጭ ያሉዋቸውን ምክረ ሀሳብም አቅርበዋል።

በዚህም ማህበረሰቡ አጫጭር ጉዞዎችን በኮሪደር ልማቱ በተሰሩ ምቹ የእግረኛ መንገዶችን እና የብስክሌት ተሽከርካሪዎችን እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል።

ሚኒስትር ዴዔታው ከአንድ ቤት እና አካባቢ የሚወጡ መኪኖዎችን የሚይዙ ሰዎች እርስ በእርስ በመተሳሰብ ቁጥራቸውን እንዲቀንሱ ጠይቀዋል። ከዚህ በተጨማሪም የኤሌክትሪክ መኪና ያላቸው ተቋማትና ግለሰቦች ቢጠቀሙ ነዳጅን መቆጠብ ይቻላል ሲሉ አስታውቀዋል።

የነዳጅ ሀብትን በቁጠባ የመጠቀም ባህል ከመቼውም ጊዜ በላይ መዳበር እንዳለበትም አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...