የነዳጅ ምርትን ለመቆጠብ ማህበረሰቡ በእግር እና የብስክሌት አማራጮችን እንዲጠቀም ጥሪ ቀረበ

Date:


በመካከለኛው ምስራቅ የተፈጠረው ቀውስ ተፅዕኖ ተከትሎ በሀገራችንና በዓለም ላይ ነዳጅን በገበያ ላይ ለማግኘት አስቸጋሪ እየሆነ መመምጣቱን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስትር ዴዔታው በርሆ ሀሰን ለኤን ቢሲ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቀውሱ ኢትዮጵያ ነዳጅ በምታጓጉዝበት የባህር ኃይል መስመር ላይ ከፍተኛ የጥቃት ተጋላጭነት እየጨመረ መጥቷል ብለዋል።

ሚኒስትር ዴታው የተፈጠረውን ወቅታዊ የነዳጅ እጥረት ተቋቁሞ ችግሩን ለመሻገር ተቋማት ማህበረሰቡ እና ለተሽከርካሪ አስመጪዎች አማራጭ ያሉዋቸውን ምክረ ሀሳብም አቅርበዋል።

በዚህም ማህበረሰቡ አጫጭር ጉዞዎችን በኮሪደር ልማቱ በተሰሩ ምቹ የእግረኛ መንገዶችን እና የብስክሌት ተሽከርካሪዎችን እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል።

ሚኒስትር ዴዔታው ከአንድ ቤት እና አካባቢ የሚወጡ መኪኖዎችን የሚይዙ ሰዎች እርስ በእርስ በመተሳሰብ ቁጥራቸውን እንዲቀንሱ ጠይቀዋል። ከዚህ በተጨማሪም የኤሌክትሪክ መኪና ያላቸው ተቋማትና ግለሰቦች ቢጠቀሙ ነዳጅን መቆጠብ ይቻላል ሲሉ አስታውቀዋል።

የነዳጅ ሀብትን በቁጠባ የመጠቀም ባህል ከመቼውም ጊዜ በላይ መዳበር እንዳለበትም አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...