የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት በድጋሚ ጥገናዉን ሊቀጥል ነው

Date:

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ወደብ ጋር ያገናኛል የተባለው በቱርኩ ያፒ መርከዚ ተቋራጭ ከ10 ዓመት በፊት 1.7 ቢሊየን ዶላር የተመደበለት የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት ጉዳቱ ተጠንቶ ተለይቷል ተባለ።

በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከፍተኛ ዝርፊያ ተፈፅሞበታል የተባለው፤ ስራውም ተቋርጦ የቆየው ይህ ፕሮጀክት እንደገና ለመቀጠልም ስራ መጀመሩ ተሰምቷል።

ባቡሩ ከጦርነት እና ግጭት ባለፈ በተፈጥሮ፤ መሬት መንቀጥቀጥ ጭምር የተወሰኑ ኪሎ ሜትሮች ጉዳት እንደደረሰበት ተረድተናል።

የዚህን ፕሮጀክት ዳግም ጀምሮ ለማጠናቀቅ ጉዳቱ እንደተለየና በእቅድ እንደተያዘ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ህሊና በላቸው ነግረውናል።

አዋሽ ወልዲያ ሀራ ገበያ የባቡር ንጣፍ መስመር ፕሮጀክት 375 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ነው።

መስመሩ ሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያን ከማእከላዊ ኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኝ ነው።

የአፋር፣ የአማራና የትግራይ ክልሎች ደግሞ ይኸው የባቡር ንጣፍ መስመር የሚያልፍባቸው ናቸው።

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ወደብ ጋር ያገናኛል የተባለው ይህ ባቡር በሰዓት 120 ኪሎ ሜትር እንዲወረወር ተደርጎ ዲዛይን የተደረገለት ነበር።

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…… https://www.mixcloud.com/ShegerFM/43t6/

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...