የኢራን መርከቦች የአሜሪካን እገዳ ለመስበር አዳዲስ ስልቶችን እየተጠቀሙ ነው

Date:

አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን የባሕር ላይ እገዳ ተከትሎ፣ ከቴህራን ጋር ግንኙነት ያላቸው መርከቦች በሆርሙዝ የባሕር መስመር ላይ ክትትልን የሚያሳስቱ የቴክኖሎጂ ስልቶችን በስፋት እየተጠቀሙ መሆኑን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል።

መርከቦቹ መገኛቸውን የሚያሳውቁ መሣሪያዎችን በማጥፋት ራሳቸውን ከራዳር ይሰውራሉ፤ አልያም ደግሞ የተሳሳተ መረጃ በመላክ ሌላ መርከብ መስለው ለመታየት ይሞክራሉ።

የባሕር ላይ ደህንነት ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ፣ መርከቦቹ የክትትል ቀጠናውን ለማለፍ የሐሰት መታወቂያዎችን በመጠቀም አሜሪካ የጣለችውን ጥብቅ ቁጥጥር እየተፈታተኑት ይገኛሉ።

ይህ አይነቱ የማታለል ስልት ቀደም ሲል በሩሲያ መርከቦች ላይ ይስተዋል የነበረ ሲሆን፣ አሁን ግን በሆርሙዝ የባሕር መስመር ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ ታውቋል።

ይህም የንግድ መርከቦችን እንቅስቃሴ በትክክል ለመከታተል አስቸጋሪ ከማድረጉም ባለፈ፣ በዓለም አቀፍ የውኃ መስመር ላይ ከፍተኛ አለመረጋጋትና እርግጠኛ አለመሆንን እየፈጠረ ነው።

መርከቦቹ እንዲህ ያለውን አደገኛ የ”ድብብቆሽ” ጨዋታ የሚጫወቱት የአሜሪካን ወታደራዊ እገዳ ጥሰው የነዳጅና የምግብ ምርቶችን ለማጓጓዝ መሆኑን የባሕር ላይ መረጃ ተንታኞች ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...

በ’ፊንቴክ’ የማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ቀጠሮ ተሰጠ

በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ስም በተፈጸመ  የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር...

የጣሊያን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያደረጉት የኢንቨስመንት መጠን 723 ሚሊዮን ዩሮ መድረሱ ተሰማ

ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች  በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን...

የቴሌግራም ማስጠንቀቂያ

ቴሌግራም (Telegram) ኦፊሴላዊ ያልሆኑ የቴሌግራም መተግበሪያዎችን (Unofficial Apps) በሚጠቀሙ...