የኢትዮጵያ የፋይናንስ ሥርዓት ጠንካራ መረጋጋትና ዕድገት ማስመዝገቡን ተገለፀ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሐምሌ 2024 እስከ ሰኔ 2025 ያለውን የሥራ ዘመን የሚዳስሰውን ሦስተኛውን የፋይናንስ መረጋጋት ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

ባንኩ በሕግ የተሰጠውን የፋይናንስ ሥርዓቱን ደኅንነትና መረጋጋት የመጠበቅ ኃላፊነት መሠረት በማድረግ ያወጣው ይህ ሪፖርት፣ በኢኮኖሚው ውስጥ ያሉ ሥጋቶችንና ተጋላጭነቶችን በጥልቀት የገመገመ ሲሆን፣ ለፖሊሲ አውጪዎችና ለባለሀብቶችም ግልጽ መረጃ ሰጥቷል።

ባለፈው በጀት ዓመት የዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ ሁኔታ ፈታኝ የነበረ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ አመልካቾች ግን መሻሻል አሳይተዋል። የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት እየጠነከረ መምጣቱና የዋጋ ግሽበት መቀነሱ ለፋይናንስ ተቋማት ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠሩ ተገልጿል።

በተለይም የመንግሥት የበጀት ጉድለትና የሀገር ውስጥ ዕዳ መቀነሱ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ ሊፈጠር የሚችለውን ተጋላጭነት ቀንሶታል።

የባንክ ዘርፉን በተመለከተ፣ ዘርፉ አስተማማኝና ዝቅተኛ ሥጋት ያለበት ሆኖ መቆየቱ ተረጋግጧል። የባንኮች የካፒታል አቅም፣ የንብረት ጥራትና ትርፋማነት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር መሻሻል አሳይቷል።

ሊያጋጥሙ የሚችሉ የብድርና የውጭ ምንዛሬ ሥጋቶችን ለመቋቋም የተደረጉ የጥንካሬ ልኬቶች (Stress tests) እንደሚያሳዩት፣ ባንኮቹ ድንገተኛ ችግሮችን የመቋቋም ሙሉ ብቃት አላቸው።

በተለይም በሀገሪቱ ብቸኛው “ሥርዓታዊ ፋይዳ ያለው ባንክ” የተሰኘው ተቋም ሁሉንም የጥንካሬ ልኬቶች ማለፉ የዘርፉን መረጋጋት አመላካች ሆኗል።


በሌላ በኩል፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ መሆኑ ተጠቁሟል። በበጀት ዓመቱ ውስጥ የተፈጸሙ የዲጂታል ግብይቶች ዋጋ ወደ 18.5 ትሪሊዮን ብር በማደግ በእጥፍ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።

ይህ ዕድገት የፋይናንስ ተደራሽነትን ቢያሻሽልም፣ ከሳይበር ጥቃትና ከማጭበርበር ጋር የተያያዙ ሥጋቶችንም ይዞ መጥቷል። በመሆኑም የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማትንና የሥጋት መከላከያ መንገዶችን ማጠናከር እንደሚገባ ባንኩ አሳስቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...