የኤርትራ መንግስት 78 ታጋቾችን መልቀቁን የማእከላዊ ትግራይ ዞን ፖሊስ አረጋገጠ

Date:

ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ትላንት ዘሀበሻ ዘገባ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ የማእከላዊ ትግራይ ዞን ፖሊስ ዛሬ እንደገለፀው የተለቀቁት በአዲቋላ ራማ በኩል ነው፡፡

የፖሊስ ኮሚሽነሩ ኮማንደር ፀጋይ አስፍሀ በሰጡት መግለጫ ከተለቀቁት ውስጥ አብዛኛዎቹ ተወልደው ያደጉት በኤርትራ መሆኑን ገልፀው እድሜያቸውም ከ45 አመት በታች መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የተወሰኑት ከኤርትራዊያን ጋር ተጋብተው ሀብትና ንብረት ያፈሩ መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡

ከዚህ ቀደም የኤርትራ መንግስት በርካታ የትግራይ ተወላጆችን አግቶ መውሰዱ በስፋት ሲገለፅ የቆየ ሲሆን ኮማንደር ፀጋይ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት 272 የትግራይ ተወላጆች በኤርትራ እስር ቤት እንደሚገኙ ከተለቀቁት ሰዎች ሰምተዋል፡፡

የተለቀቁት በአሁኑ ወቅት በራማ እንደሚገኙና በቅርቡ ወደቤተሰቦቻቸው እንደሚቀላቀሉ ያስታወቁት ኮማንደሩ ጨምረውም ‹‹የኤርትራ መንግስት እነዚህን ታጋቾች የለቀቀው የትግራይ ባለስልጣናትን ሳያማክር በራሱ ፍላጎት ነው›› ብለዋል፡፡ እነዚህ ታጋቾች መለቀቃቸውን በተመለከተ እስካሁን የኤርትራ መንግስት ያለው ነገር የለም፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...