“የግብር ክሊራንስ” የምስክር ወረቀት የብድር መከልከያ ምክንያት መሆን የለበትም

Date:

የገቢዎች ሚኒስቴር ባንኮች የግብር ክሊራንስ የምስክር ወረቀት ይዘው ለብድር ለሚቀርቡ ደንበኞች የተለመደውን የብድር አገልግሎት እንዳይከለክሉ ማሳሰቢያ መስጠቱ ተመላክቷል።

ሚኒስቴሩ በቅርቡ በሚሰጠው የምስክር ወረቀት ላይ የተቀመጠው የታክስ ቅድሚያ መብት ድንጋጌ የብድር አሰጣጥ ሂደቱን የሚቀይር አዲስ መብት አለመሆኑን በማስታወቅ፣ ባንኮች የምስክር ወረቀቱን ተቀባይነት እንደሌለው ሊያስቡ እንደማይገባ አስታውቋል።

የገቢዎች ሚኒስትር ለብሔራዊ ባንክ እና ለሁሉም ባንኮች በሚል በፃፈዉ ደብዳቤ ላይ እንደተመላከተዉ ግብር ክሊራንስ የምስክር ወረቀት የሚሰጠው ግብር ከፋዩ በሕጉ መሠረት የተጣለበትን ታክስ የመክፈል ግዴታ ሲወጣ መሆኑን ገልጿል።

በተጨማሪም፣ ለታክስ ባለስልጣኑ በቅድሚያ መከፈል እንዳለባቸውና በየትኛውም ህግ ወይም ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ክፍያዎች መሆናቸው በግልጽ ተቀምጧል።

ሚኒስቴሩ እየተሰጠ ባለው የታክስ ክሊራንስ የምስክር ወረቀት ላይ የሰፈረው የቅድሚያ መብት ድንጋጌ፣ ከላይ የተጠቀሰውን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ድንጋጌ ለማካተት እንጂ፣ ለባለስልጣኑ ሌላ አዲስ ልዩ መብት ለመስጠት እንዳልሆነ አብራርቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በመንገድ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ

አደጋው የደረሰው ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ...

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...