አሜሪካን እና ቴህራንን እያሸማገለ የሚገኘው የፓኪስታን ልዑካን ቡድን ቴህራን ገባ።
ከልዑካን ቡድኑ መካከል ከዚህ ቀደም ትራምፕ “የምወደው” ሲሉ የገለጿቸው ፊልድ ማርሻል አሲም ሙኒር እና የአገር ውስጥ ሚኒስትሩ ሞሺን ናቅቪ እንደሚገኙበት በመንግሥታቱ ድርጅት የፓኪስታን ተልዕኮ መግለጫ ያስረዳል።
ቀደም ሲል የኢራን መገናኛ ብዙኃን፣ ኢሪብ የዜና ወኪል የአሜሪካን መልዕክት ለማስተላለፍ እና ስለሁለተኛው ዙር ድርድር ለመነጋገር የልዑካን ቡድን ወደ ቴህራን እንደሚመጣ ዘግቦ ነበር።
አሜሪካ እና ኢራን የመጀመርያውን ዙር ድርድር ባለፈው ሳምነት መጨረሻ ላይ በኢዝላማባድ ያደረጉ ሲሆን ያለምንም ውጤት ተጠናቅቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሙሐማድ ሼህባዝ ሻሪፍ ሳዑዲ አረቢያ፣ ጂዳ ደርሰዋል።
ጽህፈት ቤታቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ አገራት የተጓዙት “በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ ለመለዋወጥ” መሆኑን ገልጿል።
