በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ የፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ ኢንተር ሚላንን 5 ለ 0 በኾነ ውጤት በመርታት ሻምፒዮን ኾኗል።
የፒኤስጂን የማሸነፊያ ግቦች ዲዚሬ ዱዌ ሁለት፣ አሽራፍ ሀኪሚ፣ ማዩሉ እና ቅቫራስኬሊያ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።
ፒኤስጂ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ማሳካት ችሏል።
ፒኤስጂ በውድድር ዓመቱ የሻምፒየንስ ሊግ፣ የፈረንሳይ ሊግ እና ኩፕ ዴ ፍራንስ ዋንጫ አሳክተዋል።
ይህንንም ተከትሎ ፒኤስጂ የሦስትዮሽ ዋንጫ ማሳካት የቻለ የመጀመሪያው የፈረንሳይ ክለብ በመኾን አዲስ ታሪክ ፅፏል።
አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ከአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ቀጥለው በሁለት ክለቦች የሦስትዮሽ ዋንጫ ያሳኩ ሁለተኛው አሰልጣኝ ኾነዋል።
