2 ሰዓት የፈጀው የፕሬዚዳንቶቹ የስልክ ውይይት

Date:

የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከ 2 ሰዓት በላይ የፈጀ የስልክ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ ላይ ትራምፕ ተኩስ አቁም ላይ መድረስ አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት ያነሱ ሲሆን፤ ፑቲን በበኩላቸው  ከዩክሬን ጋር ተኩስ ማቆም የሚቻለው ተገቢ ስምምነቶች ላይ ስንደርስ ብቻ ነው ብለዋል።

በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል የሚደረጉ ድርድሮች የተኩስ አቁምን እና ሌሎች የስምምነት መርሆዎችን ሊያካትቱ ይችላሉም ነው ያሉት።

ሩሲያ እና ዩክሬን የሚያግባቡ ነጥቦች ላይ መድረስ እንዳለባቸውም አንስተው፤ በኢስታንቡል ድርድሩ በድጋሚ መጀመሩ ሁለቱ አካላት  በትክክለኛው መንገድ ላይ መሆናቸውን ያሳይልም ብለዋል።

ፕሬዚዳንት ፑቲን ከፕሬዚዳንት ትራምፕ ጋር የተደረገውን ውይይት አድንቀው ገንቢ መሆኑን እንደጠቀሱ ታስ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...