Date:

ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ!

አዲስ አበባ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ፣ መላው የስፖርት ቤተሰብ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የከተማው ደርቢ ተጠናቀቀ።

በታላቁ የአዲስ አበባ ስታዲየም የተካሄደው የሁለቱ ግዙፎች ፍልሚያ፣ የኢትዮጵያ ቡናን የላቀ የበላይነት ባሳየ መልኩ በኢትዮጵያ ቡና 3 – 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በጨዋታው ኢትዮጵያ ቡና በወጣትና ፈጣን የቡድን ስብስቡ በመታገዝ የጨዋታውን ብልጫ በመውሰድ ነጥቡን ማሳካት ችሏል።

የግብ አግቢዎች፤ ለኢትዮጵያ ቡና፡- ኦካይ ጁል፣ ቢኒያም ጌታቸው እና ዘላለም አባተ

ለቅዱስ ጊዮርጊስ፡- ፍፁም ጥላሁን

በዛሬው ዕለት የሸገርን አውራ ጎዳናዎች በቡናማ እና አረንጓዴ/ቢጫ ቀለም በድምቀት ያጥለቀለቁት ደጋፊዎች፣ ጨዋታው ከሶስት ነጥብ በላይ የክብርና የኩራት ፍልሚያ መሆኑን ዳግም አስመስክረዋል።

ቡናማዎቹ በታክቲክ ብልጫና በቁርጠኝነት ያሳዩት ብቃት ውጤቱን እንዲቀዳጁ አድርጓቸዋል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ፓኪስታን ትክክለኛ አስታራቂ አይደለችም” ኢራን!

የኢራን ህግ አውጪ ኢብራሂም ሬዛኢ ከአሜሪካ ጋር እየተካሄደ ባለው...

በዋይት ሐውስ ዘጋቢዎች የእራት ግብዣ ላይ ስለነበረው ተኩስ የማናውቃቸው ጉዳዮች

ምንም እንኳ ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሐውስ በነበረው የእራት ግብዣ...

ትግስት አሰፋ ሪከርድ በማሻሻል አሸነፈች !

የ2026 የለንደን ማራቶን ውድድር ሲካሄድ በሴቶች ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትግስት...

በመላው ኢትዮጵያ ያሉት የግል ህክምና ተቋማት ብዛት ከ28,000 በላይ ነዉ

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ይህንን ያሉት...