Date:

ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ!

አዲስ አበባ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ፣ መላው የስፖርት ቤተሰብ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የከተማው ደርቢ ተጠናቀቀ።

በታላቁ የአዲስ አበባ ስታዲየም የተካሄደው የሁለቱ ግዙፎች ፍልሚያ፣ የኢትዮጵያ ቡናን የላቀ የበላይነት ባሳየ መልኩ በኢትዮጵያ ቡና 3 – 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በጨዋታው ኢትዮጵያ ቡና በወጣትና ፈጣን የቡድን ስብስቡ በመታገዝ የጨዋታውን ብልጫ በመውሰድ ነጥቡን ማሳካት ችሏል።

የግብ አግቢዎች፤ ለኢትዮጵያ ቡና፡- ኦካይ ጁል፣ ቢኒያም ጌታቸው እና ዘላለም አባተ

ለቅዱስ ጊዮርጊስ፡- ፍፁም ጥላሁን

በዛሬው ዕለት የሸገርን አውራ ጎዳናዎች በቡናማ እና አረንጓዴ/ቢጫ ቀለም በድምቀት ያጥለቀለቁት ደጋፊዎች፣ ጨዋታው ከሶስት ነጥብ በላይ የክብርና የኩራት ፍልሚያ መሆኑን ዳግም አስመስክረዋል።

ቡናማዎቹ በታክቲክ ብልጫና በቁርጠኝነት ያሳዩት ብቃት ውጤቱን እንዲቀዳጁ አድርጓቸዋል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...