‎8,183 ሊትር ነዳጅ ተወረሰ

Date:

‎የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ውስጥ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 8,183 ሊትር ነዳጅ መወረሱን አስታወቀ።

‎በከተማዋ ብቻ በተካሄደው በዚህ የቁጥጥር ስራ በውሃ ኮዳና ባልተፈቀዱ እቃዎች ሲጓጓዙ ከተያዙት ውስጥ 5,900 ሊትሩ ናፍጣ ሲሆን፣ ቀሪው ከ2,000 ሊትር በላይ ቤንዚንና ነጭ ጋዝ መሆኑ ተገልጿል።

‎ቢሮው በከተማዋ በሚገኙ ማደያዎች ላይ ጥብቅ ክትትል እያደረገ መሆኑን ጠቅሶ፣ ነዳጅ እያላቸው “የለንም” በሚሉና አገልግሎት በሚያቋርጡ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል። በዚህም መሠረት ባለፉት ስድስት ወራት ነዳጅ ደብቀው የተገኙ ሦስት ማደያዎች ላይ ክስ ተመስርቶ የታሸጉ ሲሆን፣ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያም ተሰጥቷቸዋል።

‎ቢሮው አክሎም “ጀነሬተር የለኝም” ወይም “መቅጃ ተበላሸ” በሚሉ ምክንያቶች አገልግሎት ማቋረጥ እንደማይቻልና ቁጥጥሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ብቻ ከ12ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አሉ

በሱዳን የሚገኘው የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ...

ትራምፕ አሜሪካ እና ኢራን “በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ” ሊወያዩ እንደሚችሉ ተናገሩ

ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል “በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት...

የኢራን ጦርነት የሚቀጥል ከሆነ የዓለም ምጣኔ ኃብት አደጋ ላይ እንደሚወድቅ አይኤምኤፍ አስጠነቀቀ

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በመካከለኛው ምሥራቅ የሚካሄደው የኢራን...

የመምህር ዘላለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የ፵ ቀን መታሰቢያ ጥሪ

​"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው!" (ምሳሌ ፲፥፯)​በሕይወትና በቃል ትምህርታቸው ብዙዎችን...