የዩናይትድ ስቴትስ የውጭጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ጋር ዛሬ ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. በስልክ መነጋገራቸውን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ዛሬ ባደረጉት የስልክ ውይይትየመረጋጋት እና የኢትዮጵያ የኤኮኖሚ እድገት እንዲሁም የአፍሪቃው ቀንድን በተመለከተ ሁለቱ ሃገራት በሚጋሯቸው ግቦች ላይ ማተኮራቸውን አመልክቷል።
በዚህ ውይይትም የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሪቢዮ ውይይት እና አካባቢያዊ መረጋጋት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት መስጠታቸውም ተጠቅሷል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረገጹ ባወጣው መረጃ ማርኮ ሩቢዮ የኢትዮጵያን የኤኮኖሚ ማሻሻያዎች ማድነቃቸውን በማመልከት፤ ለአሜሪካ የንግድ እና የመዋዕለንዋይ ፍሰት አማራጭ የመሆን አቅም ለመኖሩ አጽንኦት መስጠታቸውንም አክሎ ገልጿል።
